የአዲስ  አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ...

image description
- In pulice partspation    0

የአዲስ  አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በዛሬው ዕለት ለግንዛቤና ህብረተሰብ ተሳትፎ ባለሙያዎች የማነቃቂያ  መድረክ አዘጋጀ።

የአዲስ  አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ በዛሬው ዕለት ለግንዛቤና ህብረተሰብ ተሳትፎ ባለሙያዎች የማነቃቂያ  መድረክ አዘጋጀ።

የእለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ዶክተር እሸቱ  ለማ የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የከተማችን ፅዳት  ከጊዜ ወደ ጊዜ  እየተሻሻለ  ቢመጣም በከተማዋ የነዋሪው ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ አሁንም የሚቀሩ ስራዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።

ኤጀንሲው የከተማዋን ጽዳት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በርካታ ሞዴል ተቋማትንና ሞዴል መንደሮችን በመፍጠር  የነዋሪውን ጤና ለማስጠበቅ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል በማለት ይህ  መድረክ  የቀጣይ ሁለት ወራት የንቅናቄ ማስጀመሪያ እንደመሆኑ ለግንዛቤ ባለሙያዎቹ  የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ መልእክት አስተላልፈዋል። 

ወ/ሮ ሂክማ ኬረዲን በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ  ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ  በበኩላቸው የአዲስ አበባን ጽዳት  በዘላቂነት  ለማስቀጠል ከተማ አስተዳደሩ ሳይንሳዊ የቆሻሻ አወጋገድን በማስጀመር ከተማዋ ለነዋሪዎቿ ምቹና ተስማሚ እንድትሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል። አክለውም የከተማዋን ጽዳት ዘላቂነት ለማረጋገጥ የከተማዋን በርካታ ተቋማትና ብሎኮች ሞዴል ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
በመድረኩ ላይ ከጽዳት ጋር የተያያዙ ሙዝሙርና ሙዚቃዊ ድራማ ቀርቧል።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments